Skip to main content

በስነ-ምግባር የታነጸ አገር ተረካቢ ወጣት ለመገንባት የተቀናጀ ጥረት እንደሚያስፈልግ ተመላከተ፤ ‎

በስነ-ምግባር የታነጸ አገር ተረካቢ ወጣት ለመገንባት የተቀናጀ ጥረት እንደሚያስፈልግ ተመላከተ፤

‎ሆሳዕና ፦የካቲት/2018ዓ.ም‎

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድ ለመገንባት በትምህርት ተቋማት አካባቢ በቅንጅትና በትብብር መስራት የሚያስችል የግብ ስምምነት ተፈረመ።

‎የግብ ስምምነቱን የፈረሙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ እና የክልሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ናቸው።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ  ኃላፊ አቶ አሰፋ ደቼ ፣የግብ ስምምነቱ በስነ ምግባር የታነጸ ብቁና አምራች ዜጋ በትብብር ለመገንባት የሚያስችል ነው።

‎ስምምነቱ ትብብርና ቅንጅትን የሚያጎለብት ስለመሆኑም ያስረዱት አቶ አሰፋ፣የኮሚሽኑ ተነሳሽነት የሚበረታታ መሆኑንም ጠቁመዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር  አቶ ማሞ ቴጋ የግብ ስምምነቱ በሆሳዕና ከተማ ሲፈረም ባደረጉት ንግግር፣ስምምነቱ የትውልድ ስነ ምግባር ግንባታ ስራዎችን  ከታችኛው መዋቅር ጀምሮ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነው።

‎በቀጣይ በትምህርት ቤቶችና በኮሌጆች አካባቢ ለሚገኙ ክበባት የተለየ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ የተሻለ ግንዛቤ በሀገር ፍቅርና ለሀገሩ ሀላፊነትና ተጠያቂነት የሚወስድ በትውልዱ ውስጥ ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱንም ጠቁመዋል።

‎ሁለቱ ተቋማት በጋራ በመሆን በትምህርት ተቋማቱ የስነ ምግባር ትምህርት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚሰሩም ኮሚሽነር ማሞ አስታውቀው፣ ከመምህራንና ከተማሪዎች ጋር በቅርበት ለመስራት መታቀዱንም ጠቁመዋል።

 

Image